የስራ ማስታወቂያ

ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

አዲስ ኮንቲኔንታል የጤና አጠባበቅ ኢንስትቲዩት (አኮጤአኢ) በአዲስ አበባ ለሚያከናውነው ጥናት ከዚህ በታች ለተጠቀሰው ሥራ መደብ አመልካቾችን አወዳድሮ  ለመቅጠር ይፈልጋል።

የሥራ መደቡ፣ የምርምር ነርስ

ተፈላጊ መስፈርት፣

  • የትምህርት ዝግጅት፣ በሚድዋይፈሪ/በነርሲንግ ዲግሪ ያላት በህፃናት እድገት ክትትል እና ምዘና ላይ የስራ ልምድ ያላት ቢሆን ይመረጣል ወይም እንደተጨማሪ ነጥብ ይያዛል፡፡
  • ጾታ፡ ሴት

የቅጥሩ ዓይነት፣ የኮንትራት ቅጥር እንደአስፈላጊነቱ የሚታደስ

ደመወዝ፣  በኢንስቲትዩቱ የደመወዝ ስኬል መሠረት

የማመልከቻ ጊዜ፣ ከሚያዝያ 9 እስከ 24 ቀን 2ዐ18 ዓ.ም ሲሆን ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ማመልከቻ ደብዳቤ፣ ሲቪ(CV) እና

የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ በአካል በመቅረብ ማመልከት ወይም በኢሜል አድራሻ hraciph@gmail.com በመላክ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

በአካል የምታመለክቱ አመልካቾች በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከ2:30 እስከ 6:00 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 003 ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡                                                  

ለመረጃ ስልክ 0955333339/0116-390000 መደወል የሚቻል መሆኑን እናሳውቃለን፡